የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች
ሕዳር 8፣ | 2015 ዓ.ም – Nov 17 | 2022
The guardian
- ከተኩስ አቁም በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የምግብ እርዳታ ኮንቮይዎች ወደ ትግራይ መግባታቸውን የሚተነትን ጽሁፍ ነው
የተነሱ ነጥቦች
- በመንግስት እና በህወሓት መካከል በነበረው የሰላም ስምምነት በኋላ ለመጀመሪያ ግዜ የሰብአዊ እርዳታ ቡድኖች የጫኑ ኮንቮይዎች ወደ ትግራይ መግባታቸውን ።
- በትግራይ የሚገኙ ዶክተሮች እና የእርዳታ ሰራተኞች ሰብአዊ እርዳታ ለማግኘት እየጠበቁ ያሉ ታካሚዎች በህይወት ለማቆየት ጊዜ እየጠበዩ መሆናቸውን ።
- የተባበሩት መንግስታት የዓለም የምግብ ፕሮግራም ዋና ዳይሬክተር ዴቪድ ቤስሊ “ከባድ የምግብ እርዳታ በመያዝ የጭነት መኪናዎች ወደ ትግራይ እየገቡ ነው ማለታቸውን
- ይህ የሰላም ስምምነት ከተፈረረሙ በኋላ የመጀመሪያው እንቅስቃሴ እርዳታ መሆኑን ነው ብለዋል።
- እርዳታው መቀጠል እንዳለበት ሁለቱም ወገኖች ስምምነቱን መጠበቅ እንዳለባቸው እና የተበላሸውን መሰረታዊ አገልግሎቶች ወዲያውኑ መቀጠል እንዳለበት ።
- ባለፈው ሳምንት የዓለም ጤና ድርጅት ከፍተኛ የምግብ እና የመድኃኒት አቅርቦት እንዲደረግ መጠየቁን ።
- በመንግስት እና በህወሓት መካከል ስምምነት ቢፈራራሙ ሰብአዊ አቅርቦት መከልከሉን ክልሉን የሚቆጣጠረው ፓርቲ መናገሩን ።
- ሌሎች ግብረሰናይ ድርጅቶችም በዚህ ሳምንት የተወሰነ እርዳታ ወደ ትግራይ ማድረስ መቻላቸውን መናገራቸውን ።
- አሁን ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ትግራይ ከተማ የደረሰው የመጀመሪያው የሰብአዊነት አውሮፕላን ሽሬ ላይ የሙከራ በረራ ያረፈ ሲሆን ሁለት የጭነት መኪኖች የክልሉ ርዕሰ መዲና መቀሌ ደርሰዋል ሲል አለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ማሳወቁን ።
ሊንክ https://www.theguardian.com/world/2022/nov/16/food-aid-convoys-tigray-ethiopia-ceasefire
VOA
- የመንግስት እና የህወሓትን የሰላም ድርድር ተከትሎ ተጨማሪ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል መድረሱን የሚዘግብ ዘገባ ነው ።
የተነሱ ነጥቦች
- ተፋላሚዎቹ ወገኖች የተኩስ አቁም ስምምነት ካደረጉ በኋላ ለወራት የዘለቀው እገዳ አብቅቶ ተጨማሪ ዓለም አቀፍ ዕርዳታ ወደ ትግራይ ክልል እየደረሰ እንደሆነ ነው።
- የዩኤን የአለም የምግብ ፕሮግራም ወይም WFP እንዳስታወቀው የጭነት መኪኖቻቸው በአማራ ክልል በደቡብ በኩል በምትገኘው ጎንደር ከተማ በኩል ወደ ሰሜን ምዕራብ ትግራይ መድረሱን ።
- የረድኤት ድርጅቱ ተጨማሪ የምግብ አቅራቦት እና የህክምና መድሀኒት አቅራቦቱ በቅርቡ እንደሚቀጥል መሆኑን ።
- ከአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ወይም ICRC ሁለት የጭነት መኪናዎች የህክምና ቁሳቁስ መኪኖች የትግራይ ዋና ከተማ መቀሌ መድረሳቸውን የገለፀው ከቀናት በኋላ እንደሆነ ነው።
- በትግራይ ክልል ለሁለት ዓመታት በዘለቀው ጦርነት 2.5 ሚሊዮን የሚገመቱ ሰዎች ከቤት ንብረታቸው መፈናቀላቸው እና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች አሁን ላይ የምግብ ዕርዳታ እና ሌሎች መሰረታዊ ፍላጎቶችን እንደሚያስፈልጋቸው ።
ሊንክ https://www.voanews.com/a/more-aid-reaches-ethiopia-s-tigray-following-cease-fire/6836900.html
Garowe online
- አሜሪካ በትግራይ የሰላም ድርድር ላይ አበላሾች ላይ ማዕቀብ እጥላለው ማልቷን የሚገልፅ ጹሁፍ ነው ።
የተነሱ ነጥቦች
- የኢትዮጵያ መንግሥት ተወካይ አቶ ሬድዋን ሁሴን እና የህወሓት ተወካይ አቶ ጌታቸው ረዳ በአፍሪካ ኅብረት የሚመራው በትግራይ ክልል ለተነሳው ግጭት አሁን ላይ ስምምነት መፈራረማቸውን በሰነዱ ማፀደቃቸውን ።
- የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በቅርቡ የተፈረመውን የሰላም ስምምነት አጥፊ ናቸው በሚባሉ ሰዎች ላይ ማዕቀብ እንደምትጥል ።
- የአሜሪካ መንግስት ሁለቱም ወገኖች ሰብአዊ መብቶችን የሚጥሱ አካላት በህግ እንዲጠየቁ ከማድረግ ባለፈ ስምምነቱን ማክበር እንዳለባቸው ።
- በሰላም ድርድሩ ላይ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ እና የኬንያው አቻቸው ኡሁሩ ኬንያታ የተመራው የአፍሪካ ህብረት ቡድን የትግራይ ክልል መንግስት እና የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት የሰላም ስምምነቱ አንድ ለማድረግ መቻሉን ።
- በትግራይ ክልል የሚገኙ የአማራ እና የኤርትራ ሃይሎች ከክልሉ ካለወጡ ምን ሊፈጠር ይችላል ተብለው ለቀረበው ጥያቄ ከራሳቸው ቀድሜ መመለስ እንደማይችሉ መናገራቸውን
- በሁለቱም አካላት አልታዘዝም ለሚል ግን ማእቀቡ ከባድ እንደሆነ ነው ።
ሊንክ https://www.garoweonline.com/en/world/africa/us-to-impose-sanctions-of-saboteurs