Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ሕዳር 5፣ | 2015 ዓ.ም – Nov 14 | 2022

Foreign  Policy

  • የኢትዮጵያ አደገኛ የሰላም መንገድ የሚል ርዕስ ተሰቶት የተጻፈ ነው።

የተነሱ ነጥቦች

  • አሁን የተጀመረው የሠላም ስምምነት በኢትዮጵያ ለሁለት ዐመታት የተካሄደውን ጦርነት የሚያስቆም እንደሆነ
  •  የሠላም ስምምነቱ ጠንካራ እንዳልሆነ
  • የሠላሙ ስምምነት ውጤታማ እንዳይሆን የሚያደርጉ አንዳንድ የፖለቲካ ጉዳዮች እንዳሉ።
  • በጦርነቱ የትግራይ ክልል ከመብራት ፣ ኢንተርኔትና ባንክ አገልግሎቶች ተቋርጦ እንደነበር።
  • ስምምነቱ በዋንኝነት የትግራይን ህዝብ የሚጠቅም እንደሆነ
  • የኤርትራ መንግስት ምላሽም የሠላም ድርድሩን ውጤታማነት የሚያደናቅፍ እንደሆሚሆን የሚገልጹት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

ሊንክ   https://foreignpolicy.com/2022/11/14/ethiopia-war-peace-deal-truce-tigray-humanitarian-crisis/

Forbes

  • ፍትህና ተጠያቂነት ከሌለ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም ሊኖር አይችልም የሚል ድምዳሜን በርዕሱ የያዘ ነው ። 

የተነሱ ነጥቦች

  • በቅርቡ በመንግስትና በህወሓት መካከል የተደረገው ስምምነት የወነጀለኞች ተጠያቂነትን ያላካተተ በመሆኑ ለውጤታማነት የሚያበቃውን ተዓማኒነት ያላገኘ ስምምነት እንደሆነ
  • በጦርነቱ በሁሉም ወገኖች የተፈጸሙ ወንጀሎች ተመርምረው ውንጀለኞች ለህግ መቅረብ እንዳለባቸው።
  • በኖቬምበር 2022 መጀመሪያ ላይ የዶ/ር ዴኒስ ሙክዌጅ ፋውንዴሽን “በኢትዮጵያ ከግጭት ጋር የተያያዙ ወሲባዊ ጥቃቶችን መረዳት” የሚለውን አዲሱን ሪፖርታቸውን እንዳሳተሙ
  • ሪፖርቱ እንዳመለከተው “የኢትዮጵያ እና አጋር ኃይሎች የትግራይ ተወላጆችን ለማስወገድ እና/ወይም በግዳጅ ለማፈናቀል በሰፊው ተንቀሳቅሰው ወንጀል እንደፈጸሙ መረጃዎች እንዳሉት
  • ሪፖርቱን አሜሪካና ዩናይትድ ኪንግደም እገዛ በማድረግ እንዳሠሩት
  • የኤርትራ ወታደሮችም በትግራይ ህዝብ ላይ የወሲብ ጥቃትን ጨምሮ በብሔር የበቀል እርምጃዎች ወስደው እንደነበር ከጥቃቱ ከተረፉ ሠዎች መሰማቱ  የሚሉት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

ሊንክ  – https://www.forbes.com/sites/ewelinaochab/2022/11/13/there-can-be-no-peace-in-ethi

 Global Times  

  • በኢትዮጵያ መንግስትና ህወሓት ግጭት ለማቆም የደረሱበትን ስምምነት ለመፈጸም ቁርጠኛ እንደሆኑ የሚያብራራ ነው።

የተነሱ ነጥቦች

  • የደቡብ አፍሪካውን ስምምነት ለማስፈጸም እንዲረዳ በናይሮቢ ሌላ አጋዥ ስምምነት እንደተፈራረሙ
  • የአፍሪካ ህብረትም እስካሁን ድረሥ የሠላም ስምምነቱ ተፈጻሚነት እንንዲኖረው ከፈተኛ ድርሻ እየተጫወተ እንደሚገኝ።
  • የንጹሀንን ጥበቃና የእርዳታ ሠራተኞች ጥበቃን የሚያቀላጥፍ የጋራ ኮሚቴ በማቋቋም ለመሥራት እንደተስማሙ
  • ባስቸኳይ ተፈጻሚ መሆን እንዳለበትም የአፍሪካ ህብረቱ ሉዩ ልዑክ አደራዳሪው ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ለሚዲያ መግለጻቸው
  • ሁለቱም ካላት ሠላምን ለማምጣት ያለው መፍትሔ ስምምነቱን መፈጸም ብቻ እንደሆነ መስማማታቸው የሚሉት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

ሊንክ  https://www.globaltimes.cn/page/202211/1279419.shtml

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *