Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ሐምሌ 18፣ | 2014 ዓ.ም – July 25 |2022

Sudan Tribune

  • የአሜሪካው ልኡካን ስለትግራይ የሰላም ድርድር ለመነጋገር ወደ ኢትዮጵያ  ማቅናታቸውን  የሚዘግብ ነው።

በዘገባው የተነሱ ነጥቦች

  • የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር ከከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ጋር በህወሓትና የፌደራል መንግስት ሰላማዊ ድርድሩ ጉዳይ ላይ ለመምከር ወደ ኢትዮጵያ  መምጣታቸው
  • “ልዩ መልዕክተኛው ከጁላይ 24 እስከ ነሀሴ 1 ባለው ጊዜ ውስጥ ወደ ግብፅ፣ የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች እና ኢትዮጵያ እየተጓዙ ነው” ሲል የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቅዳሜ  መናገሩን ።
  • በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ ያደረገው ጉዞ ከ ህወሐት ጋር ያለውን ግጭት ለማስቆም መንግስትን ወደ ድርድር ጠረጴዛ ለማምጣት  አሜሪካ ግፊት ማድገር እንደምትፈልግ  ።
  • ልዩ መልዕክተኛ ሀመር ኢትዮጵያ ውስጥ በነበሩበት ወቅት በትግራይ ግጭት የተፈፀሙ የሰብአዊ መብት ረገጣ እና የመብት ጥሰቶች የሰብአዊ ርዳታ አሰጣጥ እና ተጠያቂነት ላይ ያለውን ሂደት ለመገምገም አሜሪካ ለመገምገም እድል እንደምታገኝ
  • አሜሪካ ኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ሰዎች ሁሉ ዘላቂ ሰላም፣ ደህንነት እና ብልጽግና ለማምጣት የሚካሄደውን ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ሂደት ለመደገፍ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶችን ማራመድ እንደቀጠለች ልዑኩ መናግሩን

ሊንክ    https://sudantribune.com/article261813/

Horseed Media

  • የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ወደ ኢትዮጵያ የሚያደርጉትን ጉዞ ካቋረጡ በኋላ ግብፅን ጎበኙ የሚል መልክት ያለው ነው።

በዘገባው የተነሱ ነጥቦች

  • የሶማሊያ ፌዴራላዊ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ሚስተር ሀሰን ሼክ መሀሙድ እና የልኡካን ቡድኑ ትናንት እሁድ ካይሮ  ግብጽ መግባታቸውን ።
  • የሶማሊያው ፕሬዚደንት ከግብጹ ፕሬዚደንት ጋር በሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ዙርያ ምክክር እንዳደረጉ
  • የፕሬዚዳንቱ የልዑካን ቡድን በግብፅ ውስጥ ካሉ ፖለቲከኞች እና ባለስልጣናት ጋር ጥልቅ ግንኙነት ያለው የብሔራዊ መረጃ ኤጀንሲ ዳይሬክተር ማሃድ ሞሃመድ ሳላድ እንደተገናኙ
  • ይህ የግብፅ ጉዞ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ወደ ኢትዮጵያ ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ ከተሰረዘ ከጥቂት ቀናት በኋላ የኢትዮጵያ መንግስት ጉዞው እንዲራዘምለት ጠይቆ እንደነበር።

ሊንክhttps://horseedmedia.net/somalia-president-hassan-visits-egypt-after-cancellation-trip-to-ethiopia-370470

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *