የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች
1 min read
ሕዳር 8፣ | 2015 ዓ.ም – Nov 17 | 2022
Africa news
- በትግራይ ክልል ተጨማሪ ሰብአዊ እርዳታ እየደረሰ ያለ መሆኑን የሚያሳይ የቪዲዩ የትንታኔ ዘገባ ነው
የተነሱ ነጥቦች
- በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ በትግራይ ክልል ሰብአዊ እርዳታ እንዲደረግ የሚጠይቅ ስምምነት መፈራረሙን ተከትሎ ተጨማሪ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል መድረሱን ።
- ባለሥልጣናቱ እንዳሉት 14 የሰብአዊ ርዳታ መኪናዎች በትግራይ ክልል መድረሳቸውን ከእነዚህም መካከል በርካቶቹ በጣም አስፈላጊ የሆነውን ነዳጅ እና የምግብ ዕርዳታን ከዩኤን የዓለም የምግብ ድርጅት መሆናቸውን ።
- የካቶሊክ ሚስዮናዊ አባት አልፍሬድ ለአሶሼትድ ፕሬስ እንደተናገሩት ሆስፒታሎች በቂ የመድኃኒት አቅርቦት እያገኙ እንደሆነ መናገራቸውን ።
- ትግራይ በከባድ ሰብአዊ ቀውስ ውስጥ ትገኛለች ይህም ለሁለት ዓመታት በእርዳታ ላይ የተጣለው እገዳ ምክንያት እንደሆነ ።
- እነዚህ ገደቦች የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የባለሙያዎች ቡድን የኢትዮጵያ መንግስት ምናልባት በአካባቢው ላይ ረሃብን እንደ ጦርነት ዘዴ ተጠቅሞበታል የሚል ድምዳሜ ላይ እንዲደርስ መገፋፈቱን ።
- በነበረው ጦርነት በትግራይ ብቻ 500,000 ሰዎች መፈናቀላቸውን ተከትሎ በትግራይ ክልል የድንገተኛ አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከል ባወጣው ሰነድ የሚያሳይ እንደሆነ ።
- በትግራይ አካባቢውን በጎበኙ የዩኤን ቡድኖች የተፈናቀሉ ካምፖች ውስጥ ከረሃብ ጋር የተያያዘ ሞት ሪፖርት መደረጉን ።
- በደቡብ አፍሪካ በአፍሪካ ህብረት ድጋፍ የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ክልሉ አሁንም የኢንተርኔት የስልክ እና የባንክ አገልግሎት ባይኖረውም አገልግሎቱን ወደ ትግራይ እንዲመለስ መጠየቁን ።
ሊንክ https://www.africanews.com/2022/11/21/ethiopia-more-humanitarian-aid-arrives-in-tigray-region/
Today news Africa
- ኦሉሴጎን ኦባሳንጆ ወደ 600,000 የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆችን ለገደለው የኢትዮጵያ ጦርነት ህወሓትን ተጠያቂ ማድረጉን የሚተነትን ነው ።
የተነሱ ነጥቦች
- ወደ 600,000 የሚጠጉ የትግራይ ተወላጆች ለህልፈት ሞት የዳረገው ለሁለት አመት የቆየው ጦርነት መሆኑን ።
- የቀድሞ የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት እና የአፍሪካ ህብረት ልዩ መልዕክተኛ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ እንደተናገሩት ህዝቡን ለሞት እንዲደራግ ያደረገው ህወሓት መሆኑን እና ተጠያቂ እንደሚሆን ።
- ለሴማፎር ተብሎ በሚጠራው አዲስ የአሜሪካ ህትመት ላይ ባወጣው አስተያየት ኦባሳንጆ የሰላም ፈጣሪነት ሚናውን እና በደቡብ አፍሪካ የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ ያጋጠሙትን ችግሮች ።
- በመንግስት እና በህወሓት መካከል በነበረው ጦርነት በአራት ክልሎች ማለትም በትግራይ በአማራ አፋር በኦሮሚያ ላይ እንደቀጠለ ። ።
- ኦባሳንጆ አክለውም እንደ ኤርትራ እና ሱዳን ያሉ አንዳንድ የኢትዮጵያ ጎረቤቶች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በጦርነቱ ውስጥ የበኩላቸውን ድርሻ ወስደዋል እና ሁሉም የቀንዱ ሀገራት በማህበራዊ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ውድቀቶች በተዘዋዋሪ መጎዳታቸውን ።
- ፕሬዚዳንት ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ በአፍሪካ ቀንድ የአፍሪካ ህብረት መልዕክተኛ እና የኢትዮጵያን የሰላም ድርድር በበላይነት መቆጠቀጠራቸውን ።
- ባለፉት አስራ አምስት ወራት ውስጥ በአፍሪካ ቀንድ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ ሆኜ ሰላምን ደህንነትን እና መረጋጋትን ለማስፈን እየሰራሁ ነው ሲሉ መናገራቸውን ።
- በተጨማሪም በስልታዊ አቋሟ እና በትግራይ ክልል የተነሳው ግጭት ትኩረቱ እና ፍፃሜው ኢትዮጵያ እንደሆነች ።
Sudan tribune
- የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የሱዳን ከፍተኛ ባለስልጣን በሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ መወያየታቸውን የሚዘግብ ጽሁፍ ነው
የተነሱ ነጥቦች
- የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ የኢጋድ ሀገራትን እየጎበኙ ከሚገኙት የሱዳን ወታደራዊ መሪ የሽግግር ምክር ቤት አባል ኢብራሂም ጋቢር ጋር በሁለትዮሽ ግንኙነት ዙሪያ መወያየታቸውን ።
- የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ እና በጄኔራል ጋቢር የተመራ የሱዳን ልዑካን ቡድን በሁለትዮሽና በሁለቱ ሀገራት ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን ።
- ስብሰባው የሱዳን እና የኢትዮጵያ የስለላ ኤጀንሲዎች በሁለቱ ሀገራት መካከል በፀረ ሽብር እና ወንጀል ላይ የመረጃ ልውውጥን ለማሳደግ ስምምነት መፈራረማቸውን ።
- የኢትዮጵያ ብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ድንቁ በካርቱም ያደረጉትን የሁለት ቀናት የስራ ጉብኝት ማጠናቀቃቸውን
- የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ተመስገን ጥሩነህ ከሱዳኑ አቻቸው አህመድ ኢብራሂም ሙፋዳል የኢንተለጀንስ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ጋር መወያየታቸውን ።
- የሱዳን ምክትል ወታደራዊ መሪ ሌተናል ጀነራል መሀመድ ሃምዳን ዳጋሎ ከኢትዮጵያ ባለስልጣን ጋር መገናኘታቸውን ።
- የኢትዮጵያ መረጃ ዳይሬክተር ለጄኔራል ዳግሎ በፌዴራል መንግስት እና ህወሀት መካከል የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ ስለ ሀገራቸው ወቅታዊ ሁኔታ ገለጻ ማድረጋቸውን ።
- በሱዳን የኢጋድ ሊቀመንበር የምስራቅ አፍሪካ ህብረት በፀጥታ፣ በኢኮኖሚ ውህደት እና ከባህላዊ ካልሆኑ አጋሮች ጋር ያለውን ትብብር ለማስፋት በሱዳን የተዘጋጀውን ፍኖተ ካርታ አስመልክቶ አቶ ጋቢር ለአህመድ ማብራሪያ መስጠታቸውን ።
ሊንክ https://sudantribune.com/article267099/