Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

መስከረም 13፣ | 2015 ዓ.ም – SEP 23 | 2022

Voa

  • በኢትዮጵያ ኦሮምያ ክልል እየተከሰተ ያለው ብጥብጥ በሺዎች የሚቆጠሩ መፈናቀል እንዳለ ቪዲዩ የሚተነትን ነው

የተነሱ ነጥቦች

  • የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኦሮሚያ ክልል በተፈጠረው ግጭት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች መፈናቀላቸውን መግለፁን ።
  • አማፂው የሸኔ ሀይል ከሰኔ ወር ጀምሮ ጥቃት እየፈፀመ ሲሆን የአማራ ክልል ሚሊሻዎች ደግሞ በሰላማዊ ሰዎች ላይ በደል ሲፈጽሙ መቆየታቸውን ።
  • በዘገባው እንዳየነው ሄንሪ ዊልኪንስ በደብረ ብርሃን የሚገኘውን የተፈናቃይ ካምፕ  መጎብኝታቸውን ።
  • ከተፈናቀሉት ውስጥ አንዳንዶቹ እንዳሉት ግጭቱን ሸሽተው የተመለሱትን ሲናገሩ በየቀኑ አዲስ መጤዎች እየመጡ እንደአሉ ነው።

 ሊንክ    https://www.voanews.com/a/spiraling-violence-in-ethiopia-oromia-region-sees-thousands-

European times

  • የአማራ ቤሔር ላይ እይተፈፀመ ያለው የተደበቀ የዘር ማጥፋት ወንጀል የሚል ትንተናነው

የተነሱ  ነጥቦች

  • በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት ሀይሎች መካከል የሰላም ድርድር እየተካሄደ ባለበት በዚህ ወቅት የአማራ ተወላጆች ላይ እየተፈፀመ ያለ ግድያ ።
  • የኢትዮጵያ አንጋፋ በሆኑት የአማራ ተወላጆች ላይ ስልታዊ እና ሆን ተብሎ የተደረገው ግድያ አሁንም በቸልተኝነት እየተፈፀመ  እንደሆነ  ።
  • በዚህ ግጭት ወቅት ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የሲቪል ማህበረሰብ ከፍተኛ ስም ያላቸው መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እዚህ ውግዘት ላይ መሳተፋቸውን ቁርጠኛ መሆናቸውን ።
  • በስዊዘርላንድ የአማራ ዘር ማጥፋት ይቁም በሚል እና ማንኛውንም አይነት መድሎ ለመታገል  ቁርጠኛ መሆናቸውን ።
  • የአማራ የዘር ማጥፋት ይቁም ከሌሎች የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ጋር በመሆን በአለም አቀፍ ማህበረሰብ ውስጥ እየደረሰ ስላለው የአማራ የዘር ማጥፋት ግንዛቤ ለመፍጠር እና እነዚህን እኩይ ተግባራት ለማስቆም  እንደሚሰራ ።
  • አለማው የአማራን ዘር ላማጥቃት በሁሉም ክልል ላይ ለተነሳው የአማራን የዘር ማጥፋት ስራ የሰባዊ መብት ተሞጋች ጨምሮ እየሰራ እንዳልሆነ
  • ነገር ግን የአለም አቀፍ ማህበረሰብ እና ሚዲያዎች ይህንን የዘር ማጥፋት ዘገባ ላለመዘገብ የመረጡት የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ሀይላቸውን በመቀላቀል የአማራ የዘር ማጥፋት ወንጀል ይቁም የሚል ማህበር እንዲፈጠር ምክንያት  እንደሆነ ነው ።
  •  የማህበሩ ዳይሬክተር እና መስራች አባል ወይዘሮ ዮዲት ጌዲዮን ማህበሩ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ በማህበሩ አመራር ላይ ሲሆኑ ማህበሩ ከሩዋንዳ እና ፈረንሳይን ጨምሮ ከተለያዩ ሀገራት የተውጣጡ የቦርድ አባላት  እንዳሉት ።

ሊንክ https://www.europeantimes.news/2022/09/amharas-the-occulted-ongoing-genocide-in-ethiopia/

UN News

  • በትግራይ ሰላማዊ ዜጎች እንደገና ወደ ማይፈታ እና ገዳይ ጦርነት ውስጥ መግባታቸውን የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ  መስማቱን ።

  የተነሱ ነጥቦች

  • የኢትዮጵያ ህዝብ በመንግስት ወታደሮች እና በህወሓት ሀይል መካከል በተፈጠረው ግጭት እንደገና በማይታለፍ እና ገዳይ መዘዞች ውስጥ እንደወደቀ  የመብት ተመራማሪዎች ማሳወቃቸውን ።
  • የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት የአለም አቀፉ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን በኢትዮጵያ ላይ በሰሜናዊ ክልል የተቀሰቀሰው ጦርነትም በሰብአዊነት ላይ ወንጀል ተፈጽሟል ብለው እንደሚያምኑ መናገራቸውን ።
  • በትግራይ ከባድ የመብት ጥሰቶች በመቀጠል ላይ ናቸው ሲል ዘገባው አክሎ  መግለፁን  
  • የአምስት ወራት የተኩስ አቁም ስምምነትን በኋላ ውጊያው ባለፈው ወር እንደገና መቀስቀሱንና ማስታወቃቸውን ።
  • የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት እንዳስታወቀው በጦርነቱ ምክንያት ከህግ-ወጥ ግድያ፣ አስገድዶ መድፈር፣ ጾታዊ ጥቃት እና በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚደርሰው ረሃብ እና ጦርነት በኢትዮጵያ ግጭቱ ከጀመረበት ጀምሮ መከሰቱን ለምክር ቤቱ ማሰማቱን ።

  ሊንክ https://news.un.org/en/story/2022/09/1127481

Africa news

  • በትግራይ ዋና ከተማ የአየር ጥቃት አንድ ሰው  መግደሉን የያዘ ዘገባ በቪዲዩ መልክ መቅረቡን

የተነሱ ነጥቦች

  • በመቀሌ ከተማ በደረሰ የአየር ጥቃት የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን  ማስታወቁን ።
  • ዛሬ ጠዋት እረፋድ ላይ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት  ማድረሱን ።
  • በመቀሌ በነበረው ግጭት የ60 አመት አዛውንት መገደላቸውን በመቀሌ የአይደር ሆስፒታል ሀላፊ የሆኑት ክብሮም ገብረስላሴ ለአጃንስ ፍራንስ ፕሬስ  መናገራቸውን ።
  • ይህ ጥቃት የደረሰው በመቀሌ ከተማ ደስታ ሆቴል አካባቢ በሰው አልባ አውሮፕላን በደረሰ ጥቃት የሞተ አስከሬን አይደር ሆስፒታል መድረሱን ሆስፒታሉ በትዊተር ገፁ  ላይ ማስታወቁን ።
  • የኢትዮጵያ መንግስት ወታደራዊ ኢላማዎችን ብቻ እንደሚያጠቃ እና የህወሓት ሀይሎች የዜጎችን ህይወት እንዲቀጥፉ በማድረግ ላይ መሆኑን በየጊዜው  የሚታይ መሆኑን ።
  • ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጦር ሰራዊቱን ልከው በህወሀት ሀይሎች ካምፖች ላይ ጥቃት ሰንዝረዋል በሚል  መከሰሳቸውን ።
  • አሁን ላይ ያለው ጦርነት የሰላም ድርድርን ጠባብ ተስፋ  ማጨለሙን ።

ሊንክhttps://www.africanews.com/2022/09/23/ethiopia-one-killed-in-air-strike-on-tigray-capital/

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *