Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

መስከረም 8፣ | 2015 ዓ.ም – SEP 18 | 2022

Reuters

  • በኢትዮጵያ ጦርነት ለመሳተፍ ኤርትራ ለሰራዊቷ ጥሪ እንዳቀረበች የካናዳ መንግስት መግለፁን የሚመለከት ነው ።

 የተነሱ ነጥቦች

  • በመንግስት እና በህወሓት መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት ምክንያት ኤርትራ የታጣቂ ሃይሎችን በማሰባሰብ ላይ እንደምትገኝ የካናዳ መንግስት መግለፁን ።
  • በህወሓት ሀይሎች የተነሳው ጦርነቱ ሊባባስ ይችላል በሚል ስጋት በሰሜን ክልል በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎችን ያፈናቀለ እና ሰብአዊ አደጋን ማስከተሉን ።
  • የህወሓት ሀይሎች ኢትዮጵያ ለተፈጠረው ግጭት ምላሽ የታጠቁ ሃይሎችን ለማሰባሰብ አጠቃላይ ጥሪ ማቅረባቸውን መናገራቸውን  የካናዳ የጉዞ ምክር በትዊተር ገጹ  መዘገቡን ።
  • የካናዳ መንግስት በኤርትራ የሚገኙ ዜጎቹ እንቅስቃሴያቸውን እንዲገድቡ እና የሀገር ውስጥ ሚዲያዎችን እንዲከታተሉ  ማሳሰቡን ።
  • የአፍሪካ ቀንድ ዲፕሎማት ለሮይተርስ እንደተናገሩት “በኤምባሲዎች፣ በዩኤን ግቢዎች እና መኖሪያ ቤቶች ውስጥ ያሉ ጠባቂዎች ሰፊ በሆነው የውትድርና ግዳጅ ከሃላፊነታቸው ይወሰዳሉ የሚል ስጋት  እንደነበራቸው ።

ሊንክ     https://www.reuters.com/world/eritrea-issues-army-mobilisation-call-ethiopia-fighting-resumes-

Egypt independent

  • የህወሓት ሃይሎች አፋጣኝ የተኩስ አቁም እና በአፍሪካ ህብረት የሚመራ የሰላም ድርድር ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር መቀበላቸውን የሚተነትን ነው  ።

የተነሱ ነጥቦች

  • የህወሓት ሀይሎች ጦርነቱን ለማቆምና እና የሰላም ድርድር ለማድረግ በአፍሪካ ህብረት የሚደርገውን የሰላም ጥሪ ለመቀበል ዝግጁ እንደሆኑ ማስታወቃቸውን ።
  • ህወሓት ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በአፋጣኝ እና በጋራ ስምምነት ላይ የሚደርሰውን ጦርነት ለማቆም ዝግጁ ነን ሲል በመግለጫው  መግለፃቸውን ።
  • የህወሓት ተደራዳሪ ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ እና ጄኔራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ ሳይዘገዩ ለመሰማራት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግሯል ።
  • የፊደራል መንግስት በሰኔ ወር ከህወሓት ሀይሎች ጋር ለመደራደር ኮሚቴ  ማወቀራቸውን ።
  • የአፍሪካ ኅብረት የሕወሃትን መግለጫ በደስታ  መቀበሉን ።
  • የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሙሳ ፋቂ ማሃማት እንደገለፁት የኢትዮጵያ ሰላም ወደ ቀድሞ ሁኔታው ​​መመለስ የሚያስችል ልዩ አጋጣሚ ነው ሲሉ  መናገራቸውን ።
  • ህወሀት ከዚህ ቀደም በአፍሪካ ህብረት ሽምግልና ላይ ከፍተኛ ስጋት እንደነበረው መግለፁን ።
  • የህወሓት ሀይል ከመንግስትን ጋር ድርድር የሚያደርግው እንደ ባንክ እና ግንኙነት ያሉ ዋና ዋና አገልግሎቶችን ወደ ትግራይ እንዲመልስ  መጠየቁን ።
  • የፌደራል መንግስት ግን የአፍሪካ ህብረት ጣልቃ ከመግባቱ በፊት ምንም አይነት ቅድመ ሁኔታ መኖር እንደሌለበት  ማሳሰቡን ነው ።

ሊንክ   https://www.egyptindependent.com/tigrayan-forces-accept-immediate-ceasefire-and-au-

VOA

  • የኢትዮጵያ መንግስት የኤርትራ ጦር ሰራዊት  መጥራቱን የሚተነትን ነው።

የተነሱ ነጥቦች

  • የኤርትራ ባለስልጣናት በሰሜናዊ ክልል ዳግም ለተቀሰቀሰው ጦርነት ምላሽ ለመስጠት የታጠቁ ሀይሎቻቸው እንዲንቀሳቀሱ መጠየቃቸውን የእንግሊዝ እና የካናዳ መንግስታት ማሳወቃቸውን ።
  • በመንግስት እና በህወሀት መካከል ለሁለት አመታት የዘለቀው ጦርነት በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት የነበረውን ተስፋ  መጨለሙን ።
  • የህወሓት ቡድን የተኩስ አቁም ስምምነት በኋላ ጦርነቱ እንደገና መነሳቱን እና በአፍሪካ ህብረት የሚመራ ውይይት ለማድረግ  መዘጋጀታቸውን ።
  • የኢትዮጵያ መንግስት በአፍሪካ ህብረት ለሚመራው የሰላም ሂደት ቁርጠኛ ነኝ ከማለት ውጪ ለደረሰው ተቃውሞ በይፋ ምላሽ አለመስጠቱን ።
  • ይህን ጦርነቱ  ማን እንደ ጀመረው ሁለቱም ወገኖች አለመናገራቸውን እና ጦርነቱ ከደቡብ ትግራይ አከባቢ ወደ ሰሜን እና ምዕራብ ራቅ ካሉ ግንባሮች  አሁን ላይ መዛመቱን
  • በጦርነቱ መጀመሪያ ላይ የኢትዮጵያን ጦር ይደግፉ የነበሩ የኤርትራ ወታደሮችን ወደ ውስጥ መግባቱ እንደሚታወስ ።

ሊንክ    https://www.voanews.com/a/eritrea-calls-up-armed-forces-after-ethiopia-clashes-

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *