Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ጳጉሜ 2፣ | 2014 ዓ.ም – SEP 7 | 2022

Africa news

  • የአሜሪካ ልዑክ በኢትዮጵያ  እየተካሄደ ያለውን ግጭት ለማስቆም እየሞከሩ እንዳሉ ነው የጻፍው ።

የተነሱ ነጥቦች

  • የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር በኢትዮጵያ የተቀሰቀሰው ጦርነት በአስቸኳይ እንዲቆም እና የሰላም ድርድር እንዲጀመር ለመጥራት በቅርብ ቀናት ውስጥ እንደሚመጡ ማስታወቃቸው
  • ለወራት የዘለቀውን የተኩስ አቁም በማፍረስ ሁለቱም ወገኖች ጦርነቱን መጀመራቸው
  • ዳግም የተቀሰቀሰው ግጭት ለሰላም ድርድር ያለውን ተስፋ ቆርጦ ግጭቱ እንዳይስፋፋ ስጋት መፍጠሩ
  • የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ሚስተር ሀመር ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ  የሚገልጹ ዋና ዋና ነጥቦች አሉት

ሊንክ   https://www.africanews.com/2022/09/06/us-envoy-in-ethiopia-to-halt-ongoing-conflicts/

Alarabiya news

  • በኢትዮጵያ ኦሮሚያ ክልል የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት በዘር ላይ በተመሰረተ  በደርሠው ጥቃት 60 ሰዎች መሞታቸውን በግለጹን የተጻፈ ነው።

የተነሱ ነጥቦች

  • በኢትዮጵያ በኦሮሚያ ክልል በዘለቀው የብሔር ተኮር ጥቃት ታጣቂዎች ከ60 በላይ ሰዎችን  መግደላቸው
  • በተጨማሪም ከ20,000 በላይ መፈናቀላቸውን የሀገሪቱ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን መናገሩ
  • በኢትዮጵያ ትልቁ ብሄር የያዙት ኦሮሞ እና አማራ መሆናቸውን የታወቀ ቢሆንም እነዚህ ብሄርሰቦች ከቅርብ ጌዜ ወዲ እርስ በእርስ በፖለቲካዊ ውዝግቦች እየተባባሰ የሚሄድ ብጥብጥ  መታየቱ
  • የሸኔ ተዋጊዎች የኦቦራ ከተማን ለመያዝ አድርገዋል በማለት ለዚያም ሙከራ ባደረጉበት ወቅት በሂደቱ ሶስት የአማራ ተወላጆች መገደላቸውን ማስታወቁ
  • በሁለት ቀናት በዘለቀው ጥቃት ከ60 በላይ ሰዎች ሲገደሉ ከ70 በላይ  መቁሰላቸው
  • በተነሳው ግጭት ንብረትና ከብቶች ተዘርፈዋል ሲል የኢሰመጉ የአካባቢውን ሰዎችና ባለሥልጣናትን ጨምሮ መግለፁን ነው ።
  •  በዚህ ግጭት ምክንያት ከ20,000 በላይ ሰዎች ተፈናቅለው በኦቦራ ከተማ እንደገኙ መናገራቸው የሚሉት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

ሊንክ   https://english.alarabiya.net/News/world/2022/09/06/Ethnic-attacks-kill-60-in-Ethiopia-s

Sudan tribune

  • ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ ያለውን ግጭት ለማስቆም የምታደርገው ቀጣናዊ ጥረት እንደቀጠሉበት ነው ትንተና ያቀረበው።

የተነሱ ነጥቦች

  • ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ ያለውን ግጭት ለማስቆም ቀጠናዊ ጥረቶችን አጠናክረው በመቀጠል ለቀጠናው ሰላምና መረጋጋት ያላቸውን ሚና ከፍተኛ እንደሆነ መገለጹ
  • የደቡብ ሱዳን የጸጥታ ጉዳዮች አማካሪ ቱት ጋትሉክ ማኒሜ ለሱዳን ትሪቡን በሰጡት መግለጫ ፕሬዝዳንት ሳልቫ ኬር እና የሱዳኑ አቻቸው ጄኔራል አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን ግጭቱን ለማስቆም የሚደረገውን ጥረት ሁሉ እንደሚደግፉ  መናገራቸው
  • ሁለቱ መሪዎች ኢትዮጵያ በፀረ-ሽብርተኝነት ትግል ውስጥ ያላትን ሚና ማመናቸው
  • ሁለቱ መሪዎች እንደተናገሩት መንግስት እና ህወሓት ወደ ነበሩበት ለመመለስ እና እንዲሁም ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ቀዳሚዎቹ  መሆናቸውን መግለጻቸውን የሚገልጹ ዋና ዋና ነጥቦች አሉት

ሊንክ    https://sudantribune.com/article263733/

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *