Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ነሐሴ 24 ፣ | 2014 ዓ.ም – Aug 30 |2022

VOA

  • የህወሓት ሃይሎች በአማራ ክልል ወልዳያን እንዳልያዙ ነው የጻፈው

የተነሱ ነጥቦች

  •  ከአምስት ወራት ቆይታ በኋላ በህወሓት እና በኢትዮጵያ መንግስት መካከል አዲስ ግጭት  መቀስቀሱ
  •  አንዳንድ አለም አቀፍ ሚዲያዎች ወያኔ በአማራ ክልል ወልድያ ከተማ መግባቱን  እየዘገቡ መሆናቸው
  • የህወሓት ተወካይ ለቪኦኤ እንደተናገሩት የህወሓት ሀይሎች እስካሁን ወደ ከተማዋ  አለመግባታቸውን ይህ አባባል ውሸት እንደሆነም መናገራቸው
  • አሁን ላይ ያለው ዋና ግጭት ከሰሜን ራቅ ባለ የቆቦ ከተማ ዙሪያ እንደሆነ የሚሉት አንኳር ነጥቦች ናቸው

ሊንክ   https://www.voanews.com/a/tigrayan-forces-deny-taking-town-in-amhara-region-

Tele SUR English

  • የመብት ተሟጋቾች በኢትዮጵያ ያለው ግጭት እንዲቆም  መጠየቃቸው ላይ የተጻፈ ነው።

ተነሱ ነጥቦች

  •  የኢትዮጵያ አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ኤክስፐርቶች ኮሚሽን በኢትዮጵያ ግጭት ውስጥ ያሉ ወገኖች ግጭቱን በአስቸኳይ አቁመው ወደ ውይይት እንዲመለሱ ጥሪ  ማቅረባቸው
  • ፓርቲዎች ትግላቸውን ባስቸኳይ አቁመው እያንዳንዳቸው ወደተቀበሉት የውይይት ሂደት እንዲመለሱ  መጠየቃቸውን ።
  • ይህ ግጭት በሰላማዊ ዜጎች ላይ እየደረሰ ያለውን ችግር እንደሚያባብስ እና የከፋ አደጋም እንደሚያስከትል  ማሳሰባቸው የሚሉት አንኳር ነጥቦች ናቸው

ሊንክ   https://www.telesurenglish.net/news/Rights-Defenders-Call-for-Cessation-of-Hostilities-in-

Sudan Tribune

  • የሕወሃት ሃይሎች ከተሞችን በውግያ መያዛቸውን ምንጮች  የተገለጸ መሆኑን ነው የተጻፈው

 የተነሱነጥቦች

  • አሸባሪው ህወሓት መጠነ ሰፊ ጥቃትን ከፍቶ በመንግስት ቁጥጥር ስር ያሉ በርካታ ከተሞችን  እንደወሰደ እንዳለ እና ግጭቱ ወደ ሌሎች ከተማ ሊያመራ የሚችል እንደሆነ
  • ሁለቱም ወገኖች ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ዓለም አቀፍ ጫናዎች በፈጠሩበት ወቅት የተደረሰውን የሰብአዊ እርቅ ስምምነት መጣሳቸውን እርስ በእርስ እየተወነጃጀሉ መሆናቸውን
  • የህወሓትን ሃይሎች ወደ አጎራባች የአማራ ክልል ግዛቶች በመግባት የቆቦ እና የሮቢት  ከተሞችን ጨምሮ ስምንት ከተሞችን በቁጥጥር ስር  እንዳዋሉ መናገራቸው
  •  የመንግስት ሀይሎችም ውግያ በከፍተኛ ሁኔታ በመቀጣጠሉ ከያዙበት ቦታዎች እያፈገፈጉ እንደሆነ የሚሉት አንኳር ነጥቦች ናቸው

ሊንክ  – https://sudantribune.com/article263419/

Egypt independent

  • ኢትዮጵያ በአባይ ግድብ ላይ ከግብፅ እና ሱዳን ጋር ለመደራደር ዝግጁ መሆኗን እንደሳወቀች የተጻፈ ነው።

 የተነሱነጥቦች

  • ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት አማካኝነት በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ከግብፅ እና ሱዳን ጋር ለመደራደር ፍላጎት እንዳላት  መግለትጿ
  • በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ይበልጣል ኤመሮ በግድቡ ዙሪያ ያሉ ችግሮችን በወንድማማችነት መፍታት  እንደሚቻል መናገራቸው
  • የግድቡ የውሃ ማጠራቀሚያ ሶስተኛውን ሙሌት በተመለከተ የኢትዮጵያ አምባሳደር በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ማረጋገጣቸው
  •  በዚህ ሙሌት ላይ ሱዳንም እንደማትጎዳ እና በታችኛው ተፋሰስ አገሮች ሱዳን እና ግብፅ ላይ ምንም አሉታዊ ተጽእኖዎች  አለመኖራቸው
  • ከቀናት በፊት ካርቱም በአባይ ግድብ 20 ሚሊዮን ሱዳናውያንን አሉታዊ በሆነ መልኩ ይጎዳል በማለት ብትናገርም ይህ የሦስተኛው ሙሌት ሙሌት በሱዳን የጎርፍ አደጋን እንደቀነሰ የሚሉት አንኳር ነጥቦች ናቸው

ሊንክ    https://egyptindependent.com/ethiopia-says-ready-to-negotiate-with-egypt-sudan-over-gerd/

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *