የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች
ጥቅምት 13 -2016 | Oct 23, 2023 |
The Eastafrican
የመረጃው እንድምታ
ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ እና በጂኦፖለቲካዊ ምክንያቶች የባህር መዳረሻ እንደምትፈልግ ስትገልጽ ተፈጻሚነቱም ለድርድር ክፍት ዝግጁ እንደሆነች የገለጸች ቢሆንም ኤርትራ እንዳሳሰባት እና ግዛቷን እንደምትከላከል እንዳስጠነቀቀች ያብራራል።
AAWSAT
የመረጃው እንድምታ
ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ድርድር ላይ እንደሆኑና ውይይቱ የህዳሴውን ግድብ አመታዊ አሞላል እና አሰራሩን የሚመለከት ህግ ለማውጣት ያለመ ሲሆን ግብፅ የሦስቱንም ሀገራት መብትና ጥቅም የሚያረጋግጥ አስገዳጅ እና ሁሉን አቀፍ ስምምነት ላይ መድረሷን የሚያብራራ።
ሊንክ – https://english.aawsat.com/arab-world/4624941-egypt-sudan-ethiopia-kick-new-round-talks-over-gerd
AAWSAT
የመረጃው እንድምታ
በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ዣኦ ዚዩዋን እንዳሉት የቻይና እና ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ግንኙነት ማሻሻያ በታሪክ ትልቅ ምዕራፍ እንደሆነ በማንሳት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ሁለንተናዊ የአየር ንብረት ስትራቴጂካዊ አጋርነት አስፈላጊነት እና አብሮነትና ትብብርን አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት እንዳስገነዘቡ አና ቻይና ከጦርነቱ በኋላ ለምታካሂደው የኢትዮጵያን መልሶ ግንባታ እና የኢኮኖሚ መነቃቃት ትደግፋለች፣ ትሳተፋለች፣ በአረንጓዴ ልማት ትብብሩን ያጠናክራል፣ የኢትዮጵያን የልማት ጥረት ለማሳደግ የአለም አቀፍ ልማት ኢኒሼቲቭን ተግባራዊ እንደሚያደርግ የሚገልጽ ነው።
ሊንክ – https://english.aawsat.com/arab-world/4624941-egypt-sudan-ethiopia-kick-new-round-talks-over-gerd