Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ሰኔ 18 |  June 25, 2023

Xinhua

 ኢትዮጵያ፣ የዕርዳታ አጋሮች የምግብ ዕርዳታን አላግባብ መመዝበሩን የሚያጣራ ኮሚቴ አቋቋመች የሚል ነው።

የተነሱ ነጥቦች

  • የኢትዮጵያ መንግስት እና የእርዳታ አጋሮች የጋራ ቴክኒካል ኮሚቴ በማዋቀር የምግብ ርዳታ አላግባብ መዘዋወሩን አንድ የኢትዮጵያ ባለስልጣን እንደገለጹ
  • የኢትዮጵያ የመንግስት እንደ የተባበሩት መንግስታት የአለም የምግብ ፕሮግራም (WFP) ያሉ የእርዳታ አጋሮች እንዲታገዱ ያደረጋቸውን ህገ-ወጥ ድርጊቶች ኮሚቴው በጥልቀት እንደሚመረምር መግለጹ
  • በኢትዮጵያ ብሄራዊ የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ኮሚሽን የሚመራው ጥምር ቴክኒክ ኮሚቴ በእርዳታ ኤጀንሲዎች የምግብ ዕርዳታ እንዲቋረጥ ምክንያት የሆነውን ችግር ለመፍታት ግብአቶችን ለማቅረብ ከወዲሁ እየሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ መንገስት እንደገለጸ
  • የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴው ስራውን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ በርካታ የውይይት መድረኮችን ማካሄዱንም ዳይሬክተሩ መግለጻቸው።
  • የ WFP መግለጫ ስማቸው ያልተጠቀሰ የሀገር ውስጥ እና የውጭ አካላት የጥላቻ እና የስም ማጥፋት መረጃዎችን እያሰራጩ ነው ሲል እንደከሰሰ የሚገልጹት ዋና ውና ነጥቦች ናቸው።

The New Arab

  • 2022  በኢትዮጵያ ያለውን ጨምሮ በጦርነት እና በተፈጥሮ አደጋዎች የተፈናቀሉ 71ሚ ሰዎች ሪከርድ ተገኘ የሚል መረጃ ነው።

የተነሱ ነጥቦች

  • የውስጥ መፈናቀል ሀገሮች በራሳቸው ድንበሮች ውስጥ ለመንቀሳቀስ የተገደዱ ሰዎችን የሚያመለክት እንደሆነና የውስጥ መፈናቀል ክትትል ማዕከል ሪፖርት ወደ ተለያዩ ሀገራት የሄዱትን ግምት ውስጥ እንዳላስገባ መግለጹ
  • በዩክሬን፣ በሶሪያ፣ በኢትዮጵያ እና በሌሎችም አካባቢዎች አሁንም መፈናቀሎች እንደቀጠሉ እንደሆነ
  • የሀገሮች ውስጥ መፈናቀል መከታተያ ማዕከል በ2022 ለሶስተኛ ተከታታይ አመት የቀጠለው የአየር ሁኔታ መለዋወጥ ክስተት ለአደጋም ለመፈናቀል ዋነኛ ምክንያት አድርጎ መጥቀሱን
  • በዚህም በፓኪስታን፣ ናይጄሪያ እና ብራዚል የጎርፍ መፈናቀልን በማስመዝገብ በሶማሊያ፣ በኬንያ እና በኢትዮጵያ ለተመዘገበው አስከፊ ድርቅ አስተዋጽኦ እንዳደረገ ማመላከቱን የሚገልጹት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

ሊንክ   – http://www.milwaukeeindependent.com/newswire/report-finds-record-71m-people-internally-

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *