የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች
ሃምሌ 6 | July 13, 2023
Al Arabiya
- የግብጹ ሲሲ እና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ/ር በሱዳን ቀውስ እና በኢትዮጵያ ግድብ ላይ መወያየታቸውን የሚገልጽ ጽሁፍ ነው ።
የተነሱ ነጠቦቸ
- የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ እና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሱዳን ቀውስ፣ በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በኢትዮጵያ ግዙፉ ግድብ ላይ መወያየታቸውን የግብፅ ፕሬዝዳንት ማስታወቁን ።
- ሲሲ አህመድ በካይሮ በሚገኘው ፕሬዝዳንታዊ ቤተ መንግስት አቀባበል አድርገውላቸዋል ሲል ፕሬዝዳንቱ መናገራቸውን ።
- በሱዳን ተቀናቃኝ ኃይሎች መካከል ለ12 ሳምንታት የዘለቀው ግጭት በቀጠናው ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ ያስከተለውን ጦርነት ለማስቆም በሚቻልበት መንገድ ላይ ለመምከር ግብፅ ሐሙስ ዕለት የሱዳን ጎረቤቶች ጉባኤ እንደምታስተናግድ ።
- የሱዳን ሁለቱ ትልልቅ ጎረቤቶች ግብፅ እና ኢትዮጵያ ከቅርብ አመታት ወዲህ ከሱዳን ጋር ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው በብሉ ናይል ላይ በሚገነባው ግዙፉ የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ ዙሪያ አለመግባባት መፈጠሩን ።
ሊንክ https://english.alarabiya.net/News/north-africa/2023/07/13/Egypt-s-Sisi-and-Ethiopia-s-PM-
The New Arab
- የግብጹ ሲሲ እና የኢትዮጵያው አህመድ በሱዳን ችግር እና በግድብ ፕሮጀክት ላይ መወያየታቸውን የሚገልጽ ዘገባ ነው ።
የተነሱ ነጥቦች
- የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ ኤል ሲሲ እና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሱዳን ቀውስ፣ በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በኢትዮጵያ ግዙፉ ግድብ ላይ መወያየታቸውን የግብፅ ፕሬዝዳንት ማስታወቃቸውን ።
- ሲሲ አህመድ በካይሮ በሚገኘው ፕሬዝዳንታዊ ቤተ መንግስት አቀባበል አድርገውላቸዋል ሲል ፕሬዝዳንቱ መግለጻቸውን ።
- ግብፅ ለ12 ሳምንታት በተቀናቃኝ የሱዳን ወታደራዊ ቡድኖች መካከል በቀጣናው ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ ያስከተለውን ግጭት ለማስቆም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለመምከር የሱዳን ጎረቤቶች የመሪዎች ስብሰባ ሃሙስ እንደምታስተናግድ ።
- የሱዳን ሁለት ትላልቅ ጎረቤቶች ግብፅ እና ኢትዮጵያ ከቅርብ አመታት ወዲህ ከሱዳን ጋር ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው በብሉ ናይል ላይ በሚገነባው ግዙፉ የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ ዙሪያ ጠብ ውስጥ መግባታቸውን ።
ሊንክ https://www.newarab.com/news/egypt-ethiopia-leaders-discuss-sudan-conflict-dam
Yahoo Finance
- የመንግስታቱ ድርጅት ባለሙያዎች ኢትዮጵያ ኤርትራዊያንን ማፈናቀሏን እንድታቆም መጠየቃቸውን የሚገልጽ ጽሁፍ ነው ።
የተነሱ ነጥቦች
- የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መርማሪዎች እና ኤክስፐርቶች ቡድን ኢትዮጵያ የኤርትራውያንን መባረር እንድታቆም ሃሙስ እለት መጠየቃቸውን እና እንዲሁም የኤርትራ ስደተኞች፣ ጥገኝነት ጠያቂዎች እና ፍልሰተኞች በዘፈቀደ ማሰርን ነው ።
- በዩኤን በመወከል የመብት ጉዳዮችን ሪፖርቶችን የሚያቀርበው ቡድኑ በሰኔ ወር መጨረሻ ኢትዮጵያ የወሰደችውን “በመቶ የሚቆጠሩ ኤርትራዊያንን ማፈናቀሏን” ሲል የጠራውን መኮነኑን በመግለጫቸው በአለም አቀፍ ህግ በጋራ መባረር የተከለከለ ነው ማለታቸውን ።
- ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ማሰቃየት እና በግዳጅ መጥፋትን ጨምሮ ለሰብአዊ መብት ረገጣ መጋለጣቸውን በግለሰብ እና በተጨባጭ የአደጋ ግምገማ ሳያካሂዱ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ማደስ ነው።”
- በአለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህግ መሰረት ማንም ሰው በደል ወይም ቅጣት ሊደርስበት ወደሚችልበት ሀገር መመለስ እንደሌለበት ያለመመለስ መርህ ዋስትና እንደሚሰጥ ።
- የኢትዮጵያ ይፋዊ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰኔ 24 ቀን 200 የሚደርሱ ኤርትራውያንን በግዳጅ ወደ አገራቸው መመለሳቸውን እየተከታተለ መሆኑን ።
- የኢትዮጵያ ስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ባለፈው ወር እንደተናገረው የተባረሩት ሰዎች ስደተኞች ወይም ጥገኝነት ጠያቂዎች አይደሉም – የዩኤን ባለሙያዎች መግለጫ ከሌሎች ታማኝ ምንጮች ጋር ይቃረናል ማለታቸውን ።
- በርካታ ታማኝ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ ቡድኑ የተመዘገቡ እና ያልተመዘገቡ ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ያካተተ እንደነበረ ።
- የኢትዮጵያ ስደተኞችና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ኃላፊ አቶ ለገሰ ቱሉ እና አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ አለመስጠታቸውን ።
- የጎረቤት ኤርትራ መንግስት ለዓመታት ህዝቡን በግዳጅ የጉልበት ስራ እና ለውትድርና መመዝገብን ጨምሮ ህዝቡን ለጭቆና ሲዳረግ ቆይቷል፤ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ እና የእምነት ነፃነት ላይ ከፍተኛ እገዳ ጥሎ በርካቶች እንዲሰደዱ ማድረጉን ።
- በኢትዮጵያ መንግስት እናየትግራይ ክልል ባለስልጣናት ጋር ባካሄደው ጦርነት የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያውያን አቻዎቻቸው እና አጋር ሚሊሻዎች ጋር በመሆን በቅርብ ሁለት አመታት ውስጥ ቢዋጉም ኢትዮጵያ እና ኤርትራ የታሪክ ባላንጣዎች እንደነበሩ ነው ።
ሊንክ https://ca.finance.yahoo.com/news/un-experts-call-ethiopia-stop-104319041.