Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ሃምሌ 6 |  July 13, 2023

Al Arabiya

  • የግብጹ ሲሲ እና የኢትዮጵያ ጠ/ሚ/ር በሱዳን ቀውስ እና በኢትዮጵያ ግድብ ላይ መወያየታቸውን የሚገልጽ ጽሁፍ ነው ።

የተነሱ ነጠቦቸ

  • የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አል ሲሲ እና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሱዳን ቀውስ፣ በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በኢትዮጵያ ግዙፉ ግድብ ላይ መወያየታቸውን የግብፅ ፕሬዝዳንት ማስታወቁን ።
  • ሲሲ አህመድ በካይሮ በሚገኘው ፕሬዝዳንታዊ ቤተ መንግስት አቀባበል አድርገውላቸዋል ሲል ፕሬዝዳንቱ  መናገራቸውን ።
  • በሱዳን ተቀናቃኝ ኃይሎች መካከል ለ12 ሳምንታት የዘለቀው ግጭት በቀጠናው ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ ያስከተለውን ጦርነት ለማስቆም በሚቻልበት መንገድ ላይ ለመምከር ግብፅ ሐሙስ ዕለት የሱዳን ጎረቤቶች ጉባኤ  እንደምታስተናግድ ።
  • የሱዳን ሁለቱ ትልልቅ ጎረቤቶች ግብፅ እና ኢትዮጵያ ከቅርብ አመታት ወዲህ ከሱዳን ጋር ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው በብሉ ናይል ላይ በሚገነባው ግዙፉ የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ ዙሪያ አለመግባባት መፈጠሩን ።

ሊንክ   https://english.alarabiya.net/News/north-africa/2023/07/13/Egypt-s-Sisi-and-Ethiopia-s-PM-

The New Arab

  • የግብጹ ሲሲ እና የኢትዮጵያው አህመድ በሱዳን ችግር እና በግድብ ፕሮጀክት ላይ መወያየታቸውን የሚገልጽ ዘገባ ነው ።

የተነሱ ነጥቦች

  • የግብፅ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ ኤል ሲሲ እና የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በሱዳን ቀውስ፣ በሁለትዮሽ ግንኙነት እና በኢትዮጵያ ግዙፉ ግድብ ላይ መወያየታቸውን የግብፅ ፕሬዝዳንት  ማስታወቃቸውን ።
  • ሲሲ አህመድ በካይሮ በሚገኘው ፕሬዝዳንታዊ ቤተ መንግስት አቀባበል አድርገውላቸዋል ሲል ፕሬዝዳንቱ መግለጻቸውን ።
  • ግብፅ ለ12 ሳምንታት በተቀናቃኝ የሱዳን ወታደራዊ ቡድኖች መካከል በቀጣናው ከፍተኛ ሰብዓዊ ቀውስ ያስከተለውን ግጭት ለማስቆም በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ለመምከር የሱዳን ጎረቤቶች የመሪዎች ስብሰባ ሃሙስ እንደምታስተናግድ ።
  • የሱዳን ሁለት ትላልቅ ጎረቤቶች ግብፅ እና ኢትዮጵያ ከቅርብ አመታት ወዲህ ከሱዳን ጋር ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው በብሉ ናይል ላይ በሚገነባው ግዙፉ የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ግድብ ዙሪያ ጠብ ውስጥ መግባታቸውን ።

ሊንክ     https://www.newarab.com/news/egypt-ethiopia-leaders-discuss-sudan-conflict-dam

 Yahoo Finance

  • የመንግስታቱ ድርጅት ባለሙያዎች ኢትዮጵያ ኤርትራዊያንን ማፈናቀሏን እንድታቆም መጠየቃቸውን የሚገልጽ ጽሁፍ ነው ።

የተነሱ ነጥቦች

  • የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መርማሪዎች እና ኤክስፐርቶች ቡድን ኢትዮጵያ የኤርትራውያንን መባረር እንድታቆም ሃሙስ እለት  መጠየቃቸውን እና እንዲሁም የኤርትራ ስደተኞች፣ ጥገኝነት ጠያቂዎች እና ፍልሰተኞች በዘፈቀደ ማሰርን ነው ።
  • በዩኤን በመወከል የመብት ጉዳዮችን ሪፖርቶችን የሚያቀርበው ቡድኑ በሰኔ ወር መጨረሻ ኢትዮጵያ የወሰደችውን “በመቶ የሚቆጠሩ ኤርትራዊያንን ማፈናቀሏን” ሲል የጠራውን መኮነኑን በመግለጫቸው በአለም አቀፍ ህግ በጋራ መባረር የተከለከለ ነው ማለታቸውን ።
  • ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ማሰቃየት እና በግዳጅ መጥፋትን ጨምሮ ለሰብአዊ መብት ረገጣ መጋለጣቸውን በግለሰብ እና በተጨባጭ የአደጋ ግምገማ ሳያካሂዱ ወደ ሀገራቸው ሲመለሱ ማደስ ነው።”
  • በአለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ህግ መሰረት ማንም ሰው በደል ወይም ቅጣት ሊደርስበት ወደሚችልበት ሀገር መመለስ እንደሌለበት ያለመመለስ መርህ ዋስትና እንደሚሰጥ ።
  • የኢትዮጵያ ይፋዊ የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ሰኔ 24 ቀን 200 የሚደርሱ ኤርትራውያንን በግዳጅ ወደ አገራቸው መመለሳቸውን እየተከታተለ  መሆኑን ።
  • የኢትዮጵያ ስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ባለፈው ወር እንደተናገረው የተባረሩት ሰዎች ስደተኞች ወይም ጥገኝነት ጠያቂዎች አይደሉም – የዩኤን ባለሙያዎች መግለጫ ከሌሎች ታማኝ ምንጮች ጋር ይቃረናል ማለታቸውን ።
  • በርካታ ታማኝ ምንጮች እንደሚሉት ከሆነ ቡድኑ የተመዘገቡ እና ያልተመዘገቡ ስደተኞችን እና ጥገኝነት ጠያቂዎችን ያካተተ እንደነበረ ።
  • የኢትዮጵያ ስደተኞችና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ኃላፊ አቶ ለገሰ ቱሉ እና አቶ ተስፋሁን ጎበዛይ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ አለመስጠታቸውን  ።
  • የጎረቤት ኤርትራ መንግስት ለዓመታት ህዝቡን በግዳጅ የጉልበት ስራ እና ለውትድርና መመዝገብን ጨምሮ ህዝቡን ለጭቆና ሲዳረግ ቆይቷል፤ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ እና የእምነት ነፃነት ላይ ከፍተኛ እገዳ ጥሎ በርካቶች እንዲሰደዱ ማድረጉን ።
  • በኢትዮጵያ መንግስት እናየትግራይ ክልል ባለስልጣናት ጋር ባካሄደው ጦርነት የኤርትራ ወታደሮች ከኢትዮጵያውያን አቻዎቻቸው እና አጋር ሚሊሻዎች ጋር በመሆን በቅርብ ሁለት አመታት ውስጥ ቢዋጉም ኢትዮጵያ እና ኤርትራ የታሪክ ባላንጣዎች እንደነበሩ ነው ።

ሊንክ   https://ca.finance.yahoo.com/news/un-experts-call-ethiopia-stop-104319041.

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *