የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ሚያዚያ 30| May 8, 2023
Almayadeen
የሱዳን ድንበር የለሽ ግጭት በሚል ርዕስ የወጣ ነው።
የተነሱ ነጥቦች
- የሱዳኑ ግጭት ድንበሮችን አልፎው የመስፋፋት አዝማምያ እንዳለው
- በግጭቱ ከሱዳን በሁሉም አቅጣጭ ወደ ሱዳን ጎረቤት ሀገራት የሱዳንም ሆኑ በዚያ ያሉ የሌሎች ሀገራት ዜጎች ድንበር በመሻገር እየተሰደዱ እንደሆነ
- ቻድ የዚህ ግጭት ዋነኛ ሰለባ ልትሆን እንደምትችል።
- ኢትዮጵያም ከሱዳን ጋር ከዚህ በፊት ባላት የድንበር እና የህዳሴ ግድብ ውዝግብ የተነሳ ግጭቱ ወደ ድንበሯም ሊስፋፋ እንደሚችል።
- ከኢትዮጵያ ትግራይ ክልል ጭምር ብዛት ያላቸው ኢትዮጵያውያንም በሱዳን እንዳሉ እንደሚታወቅ
- ግጭቱ ባልተጠበቀ ሁኔታ በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ሊስፋፋ እንደሚችል
ሊንክ – https://english.almayadeen.net/news/politics/sudan:-a-borderless-conflict
DND
- የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ከግንቦት 9-11 ፓኪስታንን እንደሚጎበኙ የሚገልጽ ጸሁፍ ነው ።
የተነሱ ነጥቦች
- ኢስላማባድ፣ ፓኪስታን፡ የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ምስጋኑ አረጋ ከኦፊሴላዊው የልዑካን ቡድን ጋር ከግንቦት 9 እስከ 11 ቀን 2023 ፓኪስታንን እንደሚጎበኙ ።
- የጉብኝቱ ዋና ዋና ጉዳዮች በኢስላማባድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መከፈቱ እና በካራቺ እና በአዲስ አበባ መካከል የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቀጥታ በረራዎች መጀመሩን እንደሚጠቅሱ ነው ።
- በኢስላማባድ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ምስጋኑ አረጋ እና የፓኪስታን አቻቸው ሂና ራባኒ ካርን እነደሚከፍቱ ነው።
- የሲንዲ ዋና ሚኒስትር ይመርቃሉ በኢትዮጵያ አየር መንገድ የቀጥታ በረራ ስራውን እየሰራ ነው።
- በጉብኝቱ ወቅት ሁለቱ ወገኖች በንግድ እና በሳይንስና ቴክኖሎጂ ትብብር ላይ ያተኮሩ የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ እንደሚወያዩ ።
- የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን ጉብኝት በኢትዮጵያ እና በፓኪስታን መካከል ያለውን ወዳጅነት ለማጠናከር አዲስ መነቃቃትን ይፈጥራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ነው ።
ሊንክ https://dnd.com.pk/ethiopian-minister-of-state-for-foreign-affairs-to-visit-pakistan-on-may-9-