Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ጥር 24 ፣ | 2015 ዓ.ም – Feb. 1 | 2023

 Military Africa

  • ኢትዮጵያ የሮኬት እና የመድፍ አቅምን እንዳሳድጋለች የሚገልጽ ነው።

የተነሱ ነጥቦች

  • የኢትዮጵያ ብሄራዊ መከላከያ ሰራዊት በሩቅ የሚደርሱ ስጋቶችን ለማየትና ለመምታት በረዥም ርቀት የጦር መሣርያዎች እንዳሉት
  • ይህ ሠራዊት የምስራቅ አፍሪካ ጀግና እንደሆነና ሠራዊቱ ጊዜው የምሥራቅ አፍሪካ ክልላዊ ቀውሶችን በተሻለ ሁኔታ ለመቋቋም የመድፍ እና የሮኬት አቅሞችንና ሌሎች ስትራቴጂካዊ መሳሪያዎችን ማጠናከሩን መቀጠሉን
  • ኢትዮጵያ ወታደራዊ የማጥቃት አቅሟን በእጅጉ ለማስፋት እና የየውጭ ጠላቶቿንም ለመከላከል በእጅጉ በመዘጋጀት ላይ የምትገኘው አሁን እጅግ ዘመናዊ መሣርያዎች መታተቅ እንደጀመረች
  • ኢትዮጵያ ያቀደቻቸውና እያሳካች ካለቻቸው ውጥኖች መካክል የአጭር ርቀት ባለስቲክ ሚሳኤሎች እና የረዥም ርቀት (የሚመሩ) ሮኬቶችን መግዛት እንደነበርና ሁለቱ ከዚህ በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ገብተው እንዳልነበር።
  • ኢትዮጵያ ረዣዥም ርቀቶች ቻይናውያን ሰራሽ ግማሽ ደርዘን PHL-03 300 ሚሜ ኤምአርኤልኤስ፣ ኤ-200 የሚመራ ሮኬት መድፍ (GRA) ሲስተሞች እና ኤም-20 የአጭር ርቀት ባለስቲክ ሚሳኤሎች (SRBMs)ን መግዛቷን
  • እንደነዚህ ያሉት የጦር መሳሪያዎች ከ150 ኪ.ሜ (93 ማይል) እስከ 300 ኪ.ሜ (186 ማይል) መካከል ያለው ርቀት መወንጨፍ እንደሚችሉ

ሊንክ    – https://www.military.africa/2023/02/ethiopias-improves-rocket-and-artillery-forces-

    All Africa

  •  የሰላም ስምምነት ተፈጻሚነት የተጠናከረ ሲሄድ የትግራይ እርዳታ ተደራሽነት እንደሚሻሻል የሚተነትን ነው።

የተነሱነጥቦች

  • የሠላም ስምምነቱ ከተፈረመ ከሶስት ወራት ገደማ በኋላ ለክልሉ ነዋሪዎች ነጻነትን እያጎናጸፋቸው እንደመጣና በአብዛኛው ሰብአዊ እርዳታ በከፍተኛ ሁኔታ ወደ ክልሉ እንደገባና ለተቸገሩ በሚሊዮን የሚቆጠሩ እየደረሰ እንደሚገኝ
  • በደቡብ አፍሪካ በተፈረመው ስምምነት መሰረት ባለፉት ሳምንታት የህወሓት ሃይሎች እጃቸው ላይ የነበሩ ከባድ መሳሪያዎችን እንዳስረከቡ
  • የኤርትራ ወታደሮችም የስምምነቱ አካል እንደሆኑና በመሆኑም ከትግራይ ለቀው እየወጡ ነው ሲሉ የትግራይ ነዋሪዎች ለሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች መንገራቸው
  • ሆኖም የኤርትራ ጦር በድንበር ላይ እንደሚቆይ እና እስካሁንም ከኢትዮጵያ ምድር ሙሉ በሙሉ እንዳልወጣ አሜርካ መግለጿን የሚታወስ እንደሆነ

 ሊንክ  –  https://allafrica.com/stories/202302010036.html

 Responsible state craft

  • በአሌክስ ዲዋል የተጻፈ፣  ከትግራይ ጦርነት በኋላ ኢትዮጵያ በአደገኛ የፖለቲካ አለመረጋጋት ሁኔታ ውስጥ ግብታ እንደምትገኝ ነው የሚገልጸው።

የተነሱነጥቦች

  • አሜሪካ እና ሌሎች ለጋሾች የአብይን የግል የፖለቲካ አጀንዳ በሚያጠናክሩ መንገዶች ሀገሪቱን ከችግር ለማዳን ከሚያደርጉትን ጥረቶች መቆጠብ እንዳለባቸው
  • መንግስት ዜጎችን ያላማከሉ በቤተመንግስትና በፓርቲው ጽ/ቤቶች ጸረ ህዝብ የተቀነባበሩ ሴራዎችን እነደሚሠራ
  • የኢትዮጵያ ፖለቲካ የማይረጋጋ እንደሆነና ሁሌች ችግሮች እንደሚኖሩት
  • በጦርነቱ በትግራይ ውስጥ የዜጎች ሞት የተሻለው ግምት ከ500,000 በላይ ሲሆን ባብዛኛው በረሃብና በበሽታ እንደሆነ
  • የህወሓት አመራር ለትግራይ ህዝብ መራብና ሞት ሲል ተገዶ ወደ ሠላም እንደመጣ
  • የኢትዮጵያ ጦር በጦርነቱ 254,000 ሞት እንደደረሰበት፣
  • በኬንያ ናይሮቢ የተፈረመውን የፕሪቶሪያ ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ የተደረገው የሰላም ስምምነት ለትግራይ ህዝብ ጥቅም ሳይሆን የኢትዮጵያን ነባሩን ህገመንግስትን ለማስከበት የተቀረጸ እንደሆነ የሚሉት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

ሊንክ  –  https://responsiblestatecraft.org/2023/01/31/ethiopia-dangerously-adrift-after-tigray-war/

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *