Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ጥር 20 ፣ | 2015 ዓ.ም – Jan 28 | 2023

The Star

  •  በኢትዮጵያ ግጭት ወደተከሰተ የትግራይ ክልል በጦርነት አማካኝነት ተቋርጦ የነበረው የህዝብ ትራንስፖርት ሊቀጥል እንደሆነ የሚያስረዳ ነው።

የተነሱ ነጥቦች

  • የኢትዮጵያ መንግስት ግጭት ወደ ተከሰተብት ሰሜናዊ ምስራቅ ትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረውን የህዝብ የየብስ ትራንስፖርት አገልግሎት ለመጀመር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን እንዳሳወቀ
  • በዚህም መሠረት ከአዲስ አበባ ከተማ የየብስ ትራንስፖርት እንዲጀመር የኢትዮጵያ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር ለህዝብ ማመላለሻ ማህበራት መመሪያ መላኩን እንዳሳወቀ
  • አገልግሎቱ በክልሉ ርዕሰ መዲና መቀሌ፣ አክሱምና ሽሬ እና ሌሎች አካባቢዎች እንደሚጀመርም መገለጹ
  • በቅርቡም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ክልሉ ተቋርጦ የነበረውን በረራ እንደጀመረውም የሚታወስ መሆኑ

ሊንክ    – https://www.thestar.com.my/news/world/2023/01/28/ethiopia-to-resume-public-

AFP

  • ያኔት ድንቁ በተሰኝች አንዲት አርቲስት የተጻፈ አንድ የፌስቡክ ፖስት  ከ AFP ጋር ተደረገ የተባለው ነገር ግን  በሌለው ቃለ ምልልስ ኢትዮጵያውያንን ቀልብ ለመሳብ የሞከረ በሚል የተጻፈ ነው።

የተነሱ ነጥቦች

  • መረጃው አንድ የAFP ጋዜጠኛ ወደ ኦሮሚያ ክልል በማምራት የኦንግ ሸኔን መሪ ጃል ገመቹ አቦዬ የተባለውን ቃለ መጠይቅ እንዳደረገለት በማስመሰል የተጻፈ እንደሆነ
  • ነገር ግን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ የኦነግ ሽኔን ሃላፊ ጃል ገመቹን ቃለመጠይ እንዳላደረጉለት መግለጹ
  • ተመሳሳይ የሆኑ ልጥፎች በፌስቡክ በመጻፍ ብዙ ችግሮች በኢትዮጵያ ተፈጥረው እንደነበር መገለጹ  የሚሉት በጽሁፉ የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

 ሊንክ  – https://factcheck.afp.com/doc.afp.com.337W6F9

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *