የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ታኅሳሥ 14፣ | 2015 ዓ.ም – Dec 23 | 2022
Garowe online
- መንግስት እና የህወሓት አዛዦች በናይሮቢ የሰላም ስምምነት ላይ መገናኘታቸውን የሚተነትን ጹሁፍ ነው ።
የተነሱ ነጥቦች
- የህወሓት ከፍተኛ አዛዦች እና ከፍተኛ የመንግስት ተወካዮች በአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን አስተባባሪነት ባለፈው ወር የተፈረመውን የሰላም ስምምነት ተግባራዊ ለማድረግ በናይሮቢ መገናኘታቸው መታወቁን ።
- የህወሓት እና የኢትዮጵያ መንግስት መኮንኖች በናይሮቢ ካረን በሚገኘው የሞራን ማሰልጠኛ ማእከል እየተገናኙ መሆናቸውን ።
- በአፍሪካ ህብረት ልዑክ ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ ክትትል በሁለቱም ወገኖች በፕሪቶሪያ የተፈረመውን የሰላም ስምምነት እንደሚገመገሙ ።
- ለሶስት ቀናት በሚቆየው የምክክር መድረክ ሁለቱ ወገኖች ትጥቅ የማስፈታቱን ሂደት አፈፃፀም የውጤት ሰነድ ላይ ይወያያሉ እንዴት መሆን እንዳለበት እንደሚወያዩ መጠበቁን ።
- የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ የአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ አባላት የአሜሪካ መንግስት እና የኢጋድ የሽምግልና ልዑካን አካል በመሆን በስብሰባው ላይ እንደሚገኙ ።
- በተጨማሪም የሽምግልና ቡድኖቹ የሰላም ስምምነቱ እንዳይጣስ አስጠንቅቀዋል ተጠያቂዎቹም ማዕቀብ እንደሚጠብቃቸው በዛው መጠቆማቸውን ።
- የኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግስት ዋና ከተማዋን መቀሌን ጨምሮ ጦሩ በማይቆጣጠራቸው አካባቢዎች የተደራጁ ወንጀሎች እና ዝርፊያ ያለበትን በተጨማሪም የትግራይን ንፁሃን ዜጎች ለመጠበቅ አስፈላጊ እርምጃ እንዲወስድ በቅርቡ ማስጠንቀቁን መግለጹን ።
ሊንክ www.garoweonline.com/en/world/africa/ethiopia-tplf-commanders-meet-in-nairobi-ove
በተጨማረም እዚው ዘገባ ላይ ኢትዮጵያ ታግተው የነበሩ የጅቡቲ ወታደሮችን እንደሚለቀቁ የሚገልጽ ዘገባ ነው ።
የተነሱ ነጥቦች
- በአፍሪካ ቀንድ ሀገር በፍሩድ ታጣቂዎች እጅ የገቡ እና ታግተው የቆዩ የጅቡቲ መከላከያ ሰራዊት አባላትን በቁጥጥር ስር ያዋሉ እና በአካባቢው ከፍተኛ ውዥንብር የፈጠረባቸው የጅቡቲ መከላከያ ሰራዊት አባላት እንደሚለቀቁ ኢትዮጵያ ማስታወቆን ።
- የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ መምሪያ ጉዳዩን ከዳይሬክተሩ አቶ ፍስሃ ሸዋል ጋር ባደረጉት ንግግር መንግስት ከአፋር ክልል ባለስልጣናት ጋር በመተባበር ለሀገራቸው ተላልፈው የተሰጡ 6 የጅቡቲ ወታደሮች መለቀቃቸውን መግለፃቸውን ።
- የኢትዮጵያ ፌደራላዊ መንግስት ከጅቡቲ ጋር በሚያዋስነው ድንበር ላይ የሚከሰቱ የጸጥታ ችግሮችን ለመፍታት በቅርበት እየሰራ ሲሆን ይህም በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት የሚያደናቅፍ ሲሆን ይህም ለአስርት አመታት በጋራ ሲሰራ መቆየታቸውን ።
- የጅቡቲ መከላከያ ሚኒስቴር በጥቅምት 06 ቀን 2022 ምሽት ላይ በጋራቢስታን በሚገኘው የጅቡቲ ጦር ታጁራህ ሬጅመንት ላይ ሰባት ወታደሮች መገደላቸውን እና እነሱም አራት ወታደሮችን ማቁሰላቸውን ።
- በተጨማሪም ሌሎች ስድስት ሰዎች እንደጠፉ የጅቡቲ ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጊሌ እነዚህ ሁሉ ወንጀለኞች በህግ እንደሚጠየቁ መታሰር እና ለፍርድ እንደሚቀርቡ መናገራቸውን ።
- ለአፋር ህዝብ የራስ ገዝ አስተዳደር እዋጋለሁ የሚለው ግንባር የተሀድሶ እና ዲሞክራሲ ታጣቂ አማፂ ቡድን FRUD በሁለቱ ሀገራት ህዝቦችን እየዘረፈ እነደሚገኝ ።
ሊንክ www.garoweonline.com/en/world/africa/ethiopia-rescues-kidnapped-djiboutian-soldiers
Garowe online
- የአሜሪካ ኮንግረስማን የኢትዮጵያ አየር መንገድ በትግራይ ግጭት ተንቀሳቅሷል በሚል ማዕቀብ እንዲጣልበት መጠየቁን
የተነሱ ነጥቦች
- በአዲስ አበባ ያለው መንግስት በህዳር ወር በፕሪቶሪያ የተደረሰው የጦርነት ስምምነት የተወሰኑ መስፈርቶችን እስኪያሟላ ድረስ ዩኤስ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ብድር እንደምትከለክል ማሳሰቡን ።
- የዩኤስ ኮንግረስማን ብራድ ሼርማን ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በፃፉት ደብዳቤ እና ለንግድ ፀሃፊ ጂና ራይሞንዶ እንዲሁም የአሜሪካ የኤክፖርት ኢምፖርት ባንክ ፕሬዝዳንት ሬታ ጆ ሌዊስ በትግራይ ያልተገደበ ሰብአዊ እርዳታ እንድታገኝ መጠየቁን ።
- 100 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር 1.75 ቢሊዮን ዶላር አካባቢ ብድር ከመሰጠቱ በፊት የባንክ ኢንተርኔት እና መድኃኒት ማድረስ እንደሚኖርበት ።
- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ የመንገደኞች እና የጭነት አውሮፕላኖችን ለመግዛት 100 ሚሊዮን ዶላር የሚያቀርበውን ብድር AP089457XX ላይ እርምጃ እንድትዘገይ እናሳስባለን።
- አየር መንገዱ እራሱን በማዕቀቡ ራዳር ውስጥ ያገኘው በግጭቱ ውስጥ ሚና ስላለው ለኢትዮጵያ ጦር የሎጀስቲክስ ድጋፍ እያደረገ ነው በሚል መሆኑን ነው።
- የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመንግስት ነው ራሱ በግጭቱ ውስጥ ቀጥተኛ ተሳትፎ ማድረጉን ።
- የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላኖች አለም አቀፍ የአቪዬሽን ህግን በመጣስ በአዲስ አበባ እና በኤርትራ መካከል የጦር መሳሪያ ለማጓጓዝ ያገለግሉ ነበር ሲሉ መከራከራቸውን ።
- በደብዳቤያቸው የዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፒ ለኮንግሬስ የገቡትን ቃል ሀገሪቱ በትግራይ ያለው ግጭት ማብቂያ እስካልሆነ ድረስ የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን በገንዘብ እንደማትደግፍ ማስታወሳቸውን ።
- ሼርማን አያይዘውም ብዙዎቹ የኢትዮጵያ መንግስት የገባቸው ቃላቶች እስካሁን አለመፈጸማቸውን ።
ሊንክ www.garoweonline.com/en/world/africa/us-congressman-calls-for-sanctions-on-ethiopi
France 24
- በመንግስት እና በህወሓት መካካል በነበረው የተኩስ አቁም ክትትል ለማድረግ መስማማታቸውን የሚናገር የዘገባ ትንታና ነው
የተነሱ ነጥቦች
- የኢትዮጵያ መንግስት እና የትግራይ አማፂ ሃይሎች በሀገሪቱ ያለውን አስከፊ ጦርነት ለማስቆም የሰላም ስምምነት በሁሉም ወገኖች ዘንድ እንዲከበር የጋራ ክትትል የሚያደርግ አካል ለማቋቋም መስማማታቸውን ።
- መንግስት እና በህወሓት በነበረው የተኩስ አቁም አውጀዋል ይህም በሰሜን ትግራይ ክልል ለሁለት አመታት በዘለቀው ደም መፋሰስ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩት ህይወታቸውን ያጡበት ጦርነቱ እንዲቆም ማድረጉን ነው ።
- ከስምምነቱ ውሣኔዎች መካከል ሁለቱም ወገኖች የእርቅ መከበር እንዲያምኑ የክትትልና ተገዢነት ዘዴን ለመዘርጋት የተደነገገው ደንብ እና ጥሰቶችን ለመፍታት ነው ።
- ሂደቱን የሚደግፈው የምስራቅ አፍሪካ ህብረት የኢጋድ ስራ አስፈፃሚ አቶ ወርቅነህ ገበየሁ እንዳሉት የጋራ ክትትል መፈጠሩ የሰላም ስምምነቱንና መንፈስን ለማክበር በሁሉም አካላት ግልፅ ምስክር እንደሆነ ነው።
- የሁለቱም ወገኖች ተወካይ የኢጋድ እና የአፍሪካ ህብረት ልዑካን ጨምሮ የጋራ ኮሚቴ በማቋቋም የሰላም ስምምነቱን ለመጠበቅ እና ድንጋጌዎቹ መከበሩን እንደሚያረጋግጥ ።
- የህወሓት ባለስልጣናት ባቀረቡት የውሳኔ ሃሳብ መሰረት ሃይሎች ለህወሓት ትጥቅ መፍታት ታማኝ ሆነው እንዲቀጥሉ እና ምንም አይነት መሳሪያም ሆነ ጥይት ለአማፂያኑ እንዳይደርስ ማድረግ ከሌሎች ተግባራት መካከል አንዱ መሆኑን ነው።
ሊንክ https://www.france24.com/en/live-news/20221223-ethiopia-s-warring-parties-agr