Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ሕዳር 7፣ | 2015 ዓ.ም – Nov 16 | 2022

Reuters

  • ከተኩስ አቁም ስምምነቱ በኋላ  የመጀመርያው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርዳታ ኮንቮይ  ወደ ኢትዮጵያ ትግራይ እንደገባ የተጻፈ ነው።  

የተነሱ ነጥቦች

  • ዛሬ እሮብ ጥቅምት 07 15 የተመድ የእርዳታ ኮንቮይ ወደ ኢትዮጵያ ትግራይ መግባቱ
  • ከተኩስ አቁም ስምምነቱ በኋላ ዝግይቶ ዛሬ ገና መግባቱ
  • እርዳታው ከጦርነቱ መጀመር በኋላ መጠቀም በተተወው የአማራ ክልል የጎንደር ኮሪደር መንገድን  በመጠቀም መግባት እንደጀመረ
  • ከነሐሴ ወር ጀምሮ የትግራይ ክልል ምንም ዓይነት ዓለማቀፍ እርዳታ እንዳልደረሰው
  • የአማራና የትግራይ ክልልም የድንበር ውዝግብም በህግ አግባብ እንደሚፈታ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ መናገራቸው
  • በተጨማሪም  የአሜሪካ መንግስት የስምምነቱን ተግባራዊነት በማይፈጽሙት ላይ ማዕብ ለመጣል እንደተዘጋጀች ነው የተጻፈው።
  • ለሰብዓዊ መብት ጥሰቶችም ተጠያቂ የሚሆኑትን አካላት እንዲጠየቁ ለማድረግ ዝግጁ እንደሆነች።
  • ይህ ደግሞ ከኤርትራ ሠራዊት ከትግራይ መውጣት እንዲተገበር በቀጥታ ጫና ለማድረግ ያለመ እንደሆነ  የሚገልጹት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

ሊንክ  1  – https://www.reuters.com/world/africa/first-un-aid-convoy-since-ceasefire-e

ሊንክ   2 – https://www.reuters.com/world/africa/us-will-not-hesitate-use-sanctions-ensur

 Aljazeera

  • የኢትዮጵያ ጠ/ሚ አብይ የትግራይን ስምምነቱን በታማኝነት ተግባራዊ ለማድረግ ቈጠኛ እንደሆኑ ነው የተጻፈው።

የተነሱ ነጥቦች

  • በስምምነቱ አፈጻጸም መሠረት  ሰብአዊ እርዳታ ወደ ትግራይ እንደሚገባና  የህወሓት ታታቂዎች ትጥቅ ይፈታሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ
  • ስምምነቱን ተግባራዊ ለማድረግ የሚያግዝ ተጨማሪ ስምምነትም ጭምር መፈራረማቸው
  • በስምምነቱ መሠረት ሁለቱማ አካላት ያልተገደበ የእርዳታ መግብታ ላይ መስማማታቸው
  • የትጥቅ መፍታቱ ጉዳይም ከኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ውጭ ሌሎች ታጣቂ ሀይሎች ከክልሉ ለቀው ከወጡ በኋላ እንደሆነ እንደተስማሙ  የሚገልጹት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

ሊንክ   – https://www.reuters.com/world/africa/us-will-not-hesitate-use-sanctions-ensure-ethiop

  DW

  • የኢትዮጵያው የትግራይ ክልል እርዳታ መቀበል እንደጀመረ የተጻፈ ነው።

የተነሱ ነጥቦች

  • ከተኩስ አቁም ስምምነቱ በኋላ የመጀመርያ እርዳታ ጫኝ ተሸክርካሪዎች ወደ ክልሉ መግባታቸው
  • ሁለት የጭነት መኪናዎች የህክምና ቁሳቁሶችን፣ የአደጋ ጊዜ መድሃኒቶችን እና የቀዶ ህክምና መሳሪያዎችን የታጨቁበት ማክሰኞ ከሰአት በኋላ በትግራይ ዋና ሆስፒታል መግባታቸውን የአለም ቀይ መስቀል ኮሚቴ እንዳሳወቀ።
  • ተጨማሪ የነፍስ አድን የእርዳታ አቅርቦቶች ታሽገው በጭነት መኪና እና በአውሮፕላን ወደ ጦርነት ወደ ክልል በተቻለ ፍጥነት ለመንቀሳቀስ ዝግጁ መሆናቸውን አይሲአርሲ መግለጹ
  • ሌሎች አለም አቀፍ የረድኤት ድርጅቶችም የፀጥታ እና የጽዳት ሂደቱን ለማጠናቀቅ እየጠበቁ መሆናቸው

ሊንክ   https://www.dw.com/en/ethiopia-tigray-starts-to-receive-desperately-needed-

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *