Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

መስከረም 25፣ | 2015 ዓ.ም – Oct 5 | 2022

Reuters

  • የአፍሪካ ህብረት የፌደራል መንግስት እና የህወሓት ሀይሎች ወደ ሰላም ድርድር እንዲመጡ መጋበዙን  የሚተነትን ዘገባ ነው ።

የተነሱ ነጥቦች

  • የአፍሪካ ህብረት የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት ሃይሎችን ወደ ሰላም እንዲመጡ መጋበዙን ።
  • ጦርነቱ ለሁለት አመታት የቆየውን ግጭት ለማስቆም በደቡብ አፍሪካ የሰላም ድርድር እንዲያደርጉ ጋብዟል ሲል ሮይተርስ በላከው ደብዳቤ ማስታወቁን ።
  • በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሙሳ ፋቂ ለህወሓት ሀይል ለሆኑት ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የጻፉት ደብዳቤ  ትክክለኛነቱን ።
  • ደብዳቤው እንደተፃፈላቸው የተነገሩት ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ ሦስት የዲፕሎማቲክ ምንጮች ማረጋገጣቀቸውን ።
  • ደብዳቤ  እንደሚያሳየው ለኢትዮጵያ መንግስት  እና ለህወሓት መላኩን እንደሚያመለክት ነው ።
  • ምንጮቹ እንደሚያመለክተት ሁለቱም ወገኖች ግን እስካሁን የትኛውም ወገን መሳተፉን አላረጋገጠም ማለታቸውን ።
  • የኢትዮጵያ መንግስት እና የህወሓት ሀይል ጦርነቱ ከተነሳ ጀምሮ በሺዎች የሚቆጠሩ ንፁሀን ዜጎችን መገደላቸውን
  • መንግስት እና ህወሓት ጦርነት ለማስቆም በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ለመሳተፍ መዘጋጀታቸውን ማስታወቃቸውን ።
  • ነገር ግን  አሁንም ለአምስት ወራት በዘለቀው የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ምንም አይነት መደበኛ ውይይት አልተካሄደም እና አሁንም በትግራይ ከባድ ውጊያ  መቀጠሉን ።

ሊንክ   https://www.reuters.com/world/africa/african-union-invites-ethiopias-warring-parties-peace-

news24

  • በሰሜን ኢትዮጵያ ያለውን ጦርነት ለማስቆም ኤስኤ እና ዩኤስ እንዴት በጋራ መስራት እንዳለባቸው  የሚል ጹሁፍ ነው ።

የተነሱ ነጥቦች

  • የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሀመር በዚህ ወር ወደ ኤስኤ መምጣታቸውን ።
  • ኤስኤ በኢትዮጵያ ሞዛምቢክ እና ዚምባብዌ ላሉ ቀውሶች መፍትሄ በማፈላለግ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል ተብሎ መጠበቁን ።
  • ሀመር ከኢትዮጵያ መንግስት እና ከአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት ጋር በኢትዮጵያ እንደሚገናኙ ።
  • በትግራይ ክልል በአፍሪካ ህብረት የሚመራው የሰላም ውጥን ደቡብ አፍሪካ የካሜኦ ሚና ብቻ ሊኖራት እንደሚችል ።
  • በአሜሪካ ደቡብ አፍሪካ  እና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች የስራ ቡድን በዋሽንግተን ዲሲ ስብሰባ ላይ መገናኘታቸውን
  • አሜሪካና ደቡብ አፍሪካ በኢትዮጵያ  ያለው ጦርነት ላይ ምክክር ማድረጋቸውን ።

ሊንክ  https://www.news24.com/news24/africa/news/how-sa-and-us-are-working-together-to

Africa news

  • የፌደራል መንግስት ከህወሓት ሀይሎችጋር የሰላም ድርድር ለማድረግ መስማማቱን የሚዘግብ ዘገባ ነው

የተነሱ ነጥቦች

  • የኢትዮጵያ መንግስት በህወሓት ሀይል ጋር ከሚገኙ ታጣቂዎች ጋር ቀንና ቦታ ሳይገልጽ ከአፍሪካ ህብረት የቀረበለትን የሰላም ድርድር መቀበሉን  ማስታወቁን ።
  • የአፍሪካ ህብረት  ለመንግስት እና ለህወሓት ሀይል የሰላም ድርድር ግብዣ  መላኩን ።
  • የኢትዮጵያ መንግስትም ይህንን ግብዣ መቀበሉን እናግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ድርድር እንደሚያስፈልግ  በሚለው መርህ መሰረት መሆኑን ነው። የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ በትዊተር ገፃቸው ላይ  መናገራቸውን ።
  • የኢትዮጵያ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት በላከው መግለጫ የአፍሪካ ህብረት በግብዣው ቀን እና የውይይቱ ቦታ ቢገለጽም ዝርዝር መረጃ አልሰጠም።
  • ከኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት ጋር ግጭት ውስጥ የሚገኘው የህወሓት አማፂ ባለስልጣናት ስለግብዣው ጉዳይ አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ተጠይቀው ወዲያውኑ ምላሽ  አለመስጠታቸውን ።
  • ዝርዝሩን በተገቢው ከፓርቲዎቹ ጋር በመመካከር እናሳውቃለን ሲሉ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ቃል አቀባይ ኤባ ካሎንዶ  መናገራቸውን ።
  • የህወሓት ሀይል መሪው ደብረጽዮን ገብረሚካኤል በህወሓት እና በኢትዮጵያ መካከል ሊደረግ በታቀደው ውይይት ላይ ቢገኝ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ጦርነት ለማስቆም የተደረገው ከፍተኛ ጥረት  ሊሆን እንደሚችል ነው።

ሊንክ  https://www.africanews.com/2022/10/05/ethiopia-agrees-to-peace-talks-with-tigrayan-rebels/

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *