Ethiopian Truth Media

The Enemy Of Truth Is Blind Acceptance.

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታዎች በተመለከተ በዓለማቀፍ ሚድያዎች የወጡ የተመረጡ ዘገባዎች

ነሐሴ 23 ፣ | 2014 ዓ.ም – Aug 29 |2022

The Gurdian

  • በትግራይ የሰሞኑን ጦርነት የቀሰቀሠው ምክንያት በሚል ለመተንተን የሞከረ ጽሁፍ ነው።

የተነሱ ነጥቦች

  • በሁለቱም ወገን በጦርነት እርስ በእርስ ያለመተማመንና የመወቃቀስ ሁኔታዎች የመጀመርያ ምክንያት እንደሆነ
  • ለወራት የቆየው የነበረው የተኩሥ አቁም ሁኔታ የሠላም ተስፋ እንዲታይ አድርጎ እንደነበርና ይህ ጦርነት ያን ተስፋ ያጨለመ እንደሆነ
  • በጦርነቱ የተጓተተውን የሠላም ድርድር ችግሮችን የሚፈታ እንዳልሆነ
  • ምንም ያህል ግጭቱ ቢቀጥል ለሠላም መስፈን መፍትሔ የማይሆን እንደሆነ የሚሉት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው

ሊንክ  –  https://www.theguardian.com/world/2022/aug/27/ethiopia-airstrike-hits-playground-in-tigray-

Egypt independent

  • የመንግስት ሃይሎች እና የህወሀት ሀይሎች ሲጋጩ በኢትዮጵያ ለተኩስ አቁም የነበረው ቁርጥኝነት  መሸርሸሩን የሚተነትን ነው።

የተነሱነጥቦች

  • ለወራት በነበረው የተኩስ አቁም ስምምነቱ እንደፈረሠ የሚያመላክት ግጭት በአዲስ መልክ መቀስቀሱ
  • በዚህ ጉዳይ ላይ ሁለቱም ወገኖች ለጥቃቱ ሌላኛውን  ወገን በግጭት ቀስቃሸንነት ተጠያቂ ማድረጋቸው ።
  • የህወሀት ሀይል ረቡዕ በፌስቡክ ገፁ ላይ ባወጣው መግለጫ መንግስት ጥቃቱን ጀመርኩ ያለው ጥቃቱን ፈጽሟል ካለ በኋላ የህወሓት ሀይሎችን እንደከሰሰ እና የቶክስ አቁሙን እንዳቋረጠ
  • የመንግስት ሃይሎች  በደቡብ ትግራይ “ማጥቃት” እንደከፈቱ  ያም በአማራ ልዩ ሃይል እና ሌሎች የኢትዮጵያ ሀይሎች እንደሚታገዝ መናገሩ።
  • ከጦርንነቱ ዳግም መቀስቀስ በፊት በመንግስትም ሆን ህወሀት በግልጽ የሚታይ የሰላም ድርድር  ፍላጎት አሳይተው እንደነበር ።
  • ነገር ግን ሁለቱ ከቅርብ ሳምንታት ወዲህ ተቃራኒ መግለጫዎችን  ማውጣታቸውን  ተከትሎ አሁን ላይ ያለው ግጭት ላይ መሆናቸው የሚሉት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው

ሊንክ https://www.egyptindependent.com/ethiopias-fragile-ceasefire-ends-as-government-forces-and-

North Africa Post

  • ዩኒሴፍ በኢትዮጵያ ጦር ሃይሎች የተፈጸመውን አሰቃቂ ጥቃት በማለት የመቀሌውን የህጻናት መዋያ ተመታ በተባለው ላይ የማውገዝ ሀሳቡን አቀረበ ይላል።

የተነሱነጥቦች

  • የህወሓት ሀይሎች የአየር ድብደባ እርምጃው ንጽሁንን ኢላማ ያደረግ እንደሆነ በመግለጽ መግለጹ
  • በድብደባው ዒላማ አካባቢ የነበሩ የእርዳታ ሠራተኞችም የጸረ እየር ተኩስ ድምጽ እንደሠሙ መረጃ መስጠታቸው
  • መንግስት  ግን ንጹሀንን ዒላማ ያደረገ እርምጃ እንዳልወሰደ መግልጹ  የሚሉት ዋና ዋና ነጥቦች ናቸው።

ሊንክ- https://northafricapost.com/60266-escalating-tigray-war-unicef-condemns-deadly-attack-by-

About Post Author

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *